የዲኤች ገዳ ባለቤት የሆኑት ታዋቂው ባለሀብት አቶ ዱጉማ ሁንዴ በዛሬው ዕለት ህይወታቸው አለፈ፡፡ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሟች ባለሀብቶች ቁጥር ሦስት ደርሷል፡፡ ከሁለት ሳምንት በፊት የካንጋሮ ፎም ባለቤት ልጅ የሆኑት የአሴ ማርብልና የአሴ ሴራሚክ ባለቤት እንዲሁም የጌታነህ ትሬዲንግ ባለቤት በተለያየ ምክንያት ራሳቸውን ያጠፉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የዲኤች ገዳ ባለቤት የሆኑት አቶ ዱጉማ ሁንዴ ለህልፈተ ህይወት መዳረግ ብዙዎችን አስደንግጣDል፡፡
መንስኤውን ለማጣራት አውራምባ ታይምስ ጥያቄ ያቀረበችላቸው የሟች ቤተሰቦች ለአቶ ዱጉማ ሞት ምክንያቱ ትንታ እንደሆነ ቢገልጹም ለባለሀብቱ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ግን ከባንክ ብድር ጋር በተያያዘ ፖለቲካዊ ምክንያት እንዳለው ያላቸውን ጥርጣሬ ገልጸዋል፡፡
The Unexpected Industries Being Disrupted By 3D Printing
-
Industries once tied to large factories, expensive equipment, and long
production schedules are now exploring...
6 days ago