Saturday, January 10, 2009

ወ/ሪት ብርቱካን ከወህኒ እንዲለቀቁ

መድረክ ለዴሞክራሲያዊ ትብብር በኢትዮጵያ በሚል ጥላ ስር ተሰባስበው በአገር ውስጥ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረጉ የሚገኙት የኢትየጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ህብረት (ኢዴኃህ)፣የኦሮሞ ፌደራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ኦፌዴን)፣ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ለሉአላዊነት (ዐረና) እንዲሁም የሶማሌ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ቅንጅት(ሶዴኃቅ) በዛሬው ዕለት ለአውራምባ ታይምስ ዝግጅት ክፍል በላኩት መግለጫ ወ/ሪት ብርቱካንም ሆኑ ሌሎች የቀድሞ ቅንጅት አመራር አባላት ጥፋተኛ የተባሉበትም ሆነ ይቅርታ የተደረገላቸው ‹ህገመንግስታዊውን ስርዓት በኃይል የመለወጥ ሙከራ› በሚል ክስ መሆኑ እየታወቀ ወ/ሪት ብርቱካን በተጠቀሰው ወንጀል ዳግም ተሰማርተው እስካልተገኙ ድረስ በውጪ ሀገር በተደረገ ስብሰባ ላይ ስለ ይቅርታው አቀራረብ ከተናገሯቸው ዓረፍተ ነገሮች አንድ ሀረግ ብቻ በመምዘዝ ይቅርታ ‹አልጠየኩም› ብለዋል በሚል ይቅርታው ተነስቶ እንደገና ለእድሜ ልክ እስራት መዳረጋቸው አሳስቦናል ብለዋል፡፡
እርምጃው ከመቼውም ጊዜ በላይ በአሳሳቢ ሁኔታ እየጠበበ የመጣውን የሀገሪቱን ፖለቲካዊ ምህዳር ከድጡ ወደ ማጡ እንዳይከተው ከፍተኛ ስጋት አሳድሮብናል ያለው የፓርቲዎቹ መግለጫ ወ/ሪት ብርቱካን በተያዙበት ሰዓት አብሮአቸው በነበሩ ዜጎች ላይ ተወሰደ የተባለው ህገ ወጥ የሀይል እርምጃና እንግልት እንዳሳሰበውና በተለይ ‹ማንነታቸውን ባላሳወቁና ህጋዊ መጥሪያ ባላሳዩ ኃይሎች ተገደው እየተንገላቱ መወሰዳቸው የህግ የበላይነትን የጣሰና በብዙ ወገኖች ዘንድም ስጋት የጫረ እርምጃ ነው› ሲል ገልጻDል፡፡
ስለሆነም ይላል ይ¤ው መግለጫ ‹መንግስት ሁኔታውን እንደገና መርምሮ እና አጢኖ የተሰረዘው የወ/ሪት ብርቱካን ይቅርታ ውድቅ ሆኖ ቀደም ሲል የተሰጣቸው ይቅርታ ጸንቶ ከወህኒ እንዲለቀቁ እንዲያደርግ አበክረን እንጠይቃለን› ብሏል፡፡