የዲኤች ገዳ ባለቤት የሆኑት ታዋቂው ባለሀብት አቶ ዱጉማ ሁንዴ በዛሬው ዕለት ህይወታቸው አለፈ፡፡ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሟች ባለሀብቶች ቁጥር ሦስት ደርሷል፡፡ ከሁለት ሳምንት በፊት የካንጋሮ ፎም ባለቤት ልጅ የሆኑት የአሴ ማርብልና የአሴ ሴራሚክ ባለቤት እንዲሁም የጌታነህ ትሬዲንግ ባለቤት በተለያየ ምክንያት ራሳቸውን ያጠፉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የዲኤች ገዳ ባለቤት የሆኑት አቶ ዱጉማ ሁንዴ ለህልፈተ ህይወት መዳረግ ብዙዎችን አስደንግጣDል፡፡
መንስኤውን ለማጣራት አውራምባ ታይምስ ጥያቄ ያቀረበችላቸው የሟች ቤተሰቦች ለአቶ ዱጉማ ሞት ምክንያቱ ትንታ እንደሆነ ቢገልጹም ለባለሀብቱ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ግን ከባንክ ብድር ጋር በተያያዘ ፖለቲካዊ ምክንያት እንዳለው ያላቸውን ጥርጣሬ ገልጸዋል፡፡
Common Legal Mistakes People Make And How To Avoid Them
-
Have you ever faced legal issues or wondered if you were following the law
correctly?...
2 weeks ago