Saturday, January 10, 2009

የዲኤች ገዳ ባለቤት በድንገት አረፉ

የዲኤች ገዳ ባለቤት የሆኑት ታዋቂው ባለሀብት አቶ ዱጉማ ሁንዴ በዛሬው ዕለት ህይወታቸው አለፈ፡፡ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሟች ባለሀብቶች ቁጥር ሦስት ደርሷል፡፡ ከሁለት ሳምንት በፊት የካንጋሮ ፎም ባለቤት ልጅ የሆኑት የአሴ ማርብልና የአሴ ሴራሚክ ባለቤት እንዲሁም የጌታነህ ትሬዲንግ ባለቤት በተለያየ ምክንያት ራሳቸውን ያጠፉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የዲኤች ገዳ ባለቤት የሆኑት አቶ ዱጉማ ሁንዴ ለህልፈተ ህይወት መዳረግ ብዙዎችን አስደንግጣDል፡፡
መንስኤውን ለማጣራት አውራምባ ታይምስ ጥያቄ ያቀረበችላቸው የሟች ቤተሰቦች ለአቶ ዱጉማ ሞት ምክንያቱ ትንታ እንደሆነ ቢገልጹም ለባለሀብቱ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ግን ከባንክ ብድር ጋር በተያያዘ ፖለቲካዊ ምክንያት እንዳለው ያላቸውን ጥርጣሬ ገልጸዋል፡፡